|
|
|||
|
||||
Overviewየቅዱሳን ዘመን ስንል ምን ማለታችን ነው? በጌታ በኢየሱስ ክርስቶር ሞት ተዋጅተን በትንሣኤው ዳግም የተወለድን ሁላችን፣ አምነን የዳንን አማኞች ብቻ ሳንሆን ቅዱሳን ለመሆን ተጠርተናል (ሮሜ 1፡7 ፥ 1ቆሮ 1፡2)። ቅዱሳን ማለት ለጌታ ለራሱ የተለዩ ገንዘቡ የሆነ ሕዝብ ማለት ነው (ቲቶ 2፡14)። ቅዱሳንነት ጥሪ እንጂ ስም አይደለም። ይህም ጥሪ ለጥቂቶች ብቻ የተሰጠ ሳይሆን፣ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅነት ላመኑ ሁሉ የተሰጠ ጥሪ ነው። ቅዱሳን ለመሆን እንደተጠራን የነገረን የእግዚአብሔር ቃል፣ መጠራት ብቻ ሳይሆን በተጠራንበትም መጠራት መመላለስ እንዳለብንም ያሳስበናል (ኤፌ 4፡1)። ስለዚህም ነው ቅዱሳን የሚለው ቃል መጠሪያ ብቻ ያልሆነው። ስለዚህ የቅዱሳን ዘመን ብለን ስንናገር፣ በቅድሚያ፣ ያመንን ሁሉ፣ ቅዱሳን (የተለዩ) ለመሆን ሁላችን እንደተጠራን እውቀቱ እንዲኖረንና በተጨማሪም በተጠራንበት መጠራት መመላለስ ደግሞ ሁላችን እንደሚጠበቅብን ግንዛቤ ውስጥ እንድናስገባም ነው። እነዚህን ሁለት ነገሮች መረዳትና በእነዚህ መረዳቶችም መመላለስ የቅዱሳንን ዘመን ማምጣት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱሳን ዘመን መምጣት አብሳሪዎች እንድንሆንም ያነቃቃል። ይህ የመጀመርያ ቅጽ በሦስት ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን፣ የመጀመርያው ክፍል የእግዚአብሔርን ቅዱስነት በተመለከተ የሚናገር ነው። ስለ ቅዱሳን ከመናገራችን በፊት የእግዚአብሔርን ቅዱስነት ማየትና መመልከት አስፈላጊ ነው። በሁለተኛው ክፍል ስለ ቅዱሳን ወይም ስለ ቅዱስ ሕዝብ እንመለከታለን። ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር ነው ቅዱስ ሕዝብ ሊኖረው የሚችለው። እንዲሁም በመጨረሻው ክፍል ላይ በተለያየ ዘመን እግዚአብሔር የተለያየ የሥራ ትኩረት ሊኖረው ስለሚችል አሁን ያለው የሥራ ትኩረት ለማየት ዘመኑን ስለማወቅ እንመለከታለን። ዘመኑን ካላወቅን አሁን ያለንበትን ዘመን የቅዱሳን ዘመን ነው ልንል አንችልም። መልካም ንባብ! Full Product DetailsAuthor: Ermias TilahunPublisher: IngramSpark Imprint: IngramSpark Edition: Saints Era Volume 1 ed. Volume: 1 Dimensions: Width: 15.20cm , Height: 1.10cm , Length: 22.90cm Weight: 0.286kg ISBN: 9781087922379ISBN 10: 1087922372 Pages: 208 Publication Date: 10 September 2018 Audience: General/trade , General Format: Paperback Publisher's Status: Active Availability: In stock We have confirmation that this item is in stock with the supplier. It will be ordered in for you and dispatched immediately. Language: Amharic Table of ContentsReviewsAuthor InformationTab Content 6Author Website:Countries AvailableAll regions |